Daily Archives: 02/11/2013

የምእመናን ቆጠራና ምዝገባ በአህጉረ ስብከት ሓላፊነት ይካሄዳል: የቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ መግለጫ

  • ቅ/ሲኖዶስ ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪካዊነትና ቀዳሚነት እውነታውንና ትክክለኛውን የሚገልጽ ጽሑፍ እንዲዘጋጅ ለሊቃውንት ጉባኤው ትእዛዝ ሰጠ
  • የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት ለምልአተ ጉባኤው ስብሰባ የሰጠው ሽፋን ‹‹የጉርሻ ያህል ነው›› በሚል ተነቀፈ
  • ‹‹ጉባኤው አገር አቀፍ ብቻ ሳይኾን ዓለም አቀፍም ነው፤ የምንሰጠው ትምህርት ነው፤ የምንወድቀው የምንነሣው ስለ ሀገር ጉዳይ ነው፤ ቤተ ክርስቲያን በዐይን የሚታይ በእጅ የሚጨበጥ ታሪክ ነው ያስረከበችው፤ በምን ምክንያት ነው[የአየር ሽፋኑ]ቀለል የሚለው›› /ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ/
  • ‹‹ከባለሥልጣናት[ከመንግሥት] የምናገኛቸውን መልእክቶች እናስተላልፋለን፤ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትሩእናቶች በሆስፒታል እንዲወልዱ ደጋግማችኹ አስተላልፉን ብለው ነግረውን በቤተ ክርስቲያናችን ብዙ ሺሕ ሕዝብ በተሰበሰበበትና በየአጋጣሚው እናስተላልፋለን፤ እኛም እዚህ ስለ አገር ጉዳይ እንነጋገራለን፤ የምንነጋገረው ግን የሚተላለፈው የጉርሻ ያህል ነው፤ ለሕዝቡ እንዲተላለፍ እንጂ የሚዲያ ሱሰኛ ኾነን አይደለም፤ የሚነገረው ነገር ለሕዝቡ በአግባቡ ቢተላለፍ መልካም ነው›› /ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ/

Holy SynodTikmit Meeting

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ቆጠራና ምዝገባ በእያንዳንዱ አህጉረ ስብከት ሓላፊነት እንደሚካሄድ ቅዱስ ሲኖዶስ አስታወቀ፡፡

Continue reading

  • ቅ/ሲኖዶስ ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪካዊነትና ቀዳሚነት እውነታውንና ትክክለኛውን የሚገልጽ ጽሑፍ እንዲዘጋጅ ለሊቃውንት ጉባኤው ትእዛዝ ሰጠ
  • የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት ለምልአተ ጉባኤው ስብሰባ የሰጠው ሽፋን ‹‹የጉርሻ ያህል ነው›› በሚል ተነቀፈ
  • ‹‹ጉባኤው አገር አቀፍ ብቻ ሳይኾን ዓለም አቀፍም ነው፤ የምንሰጠው ትምህርት ነው፤ የምንወድቀው የምንነሣው ስለ ሀገር ጉዳይ ነው፤ ቤተ ክርስቲያን በዐይን የሚታይ በእጅ የሚጨበጥ ታሪክ ነው ያስረከበችው፤ በምን ምክንያት ነው[የአየር ሽፋኑ]ቀለል የሚለው›› /ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ/
  • ‹‹ከባለሥልጣናት[ከመንግሥት] የምናገኛቸውን መልእክቶች እናስተላልፋለን፤ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትሩእናቶች በሆስፒታል እንዲወልዱ ደጋግማችኹ አስተላልፉን ብለው ነግረውን በቤተ ክርስቲያናችን ብዙ ሺሕ ሕዝብ በተሰበሰበበትና በየአጋጣሚው እናስተላልፋለን፤ እኛም እዚህ ስለ አገር ጉዳይ እንነጋገራለን፤ የምንነጋገረው ግን የሚተላለፈው የጉርሻ ያህል ነው፤ ለሕዝቡ እንዲተላለፍ እንጂ የሚዲያ ሱሰኛ ኾነን አይደለም፤ የሚነገረው ነገር ለሕዝቡ በአግባቡ ቢተላለፍ መልካም ነው›› /ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ/

Holy SynodTikmit Meeting

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ቆጠራና ምዝገባ በእያንዳንዱ አህጉረ ስብከት ሓላፊነት እንደሚካሄድ ቅዱስ ሲኖዶስ አስታወቀ፡፡

‹‹ቤተ ክርስቲያን በሥሯ ያሉ ምእመኖቿን ቆጥራ መመዝገብ እንድትችል›› የሚካሄደው ይኸው ታላቅ አገራዊ ክንዋኔ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ በሚያዘጋጀው ቅጽ አማካይነት እንደሚከናወን ነው ቅዱስ ሲኖዶሱ የገለጸው፡፡

Continue reading

ቅዱስ ሲኖዶስ ለ‹‹ገለልተኛ›› አብያተ ክርስቲያን ጥሪ ያደርጋል

  • የአቡነ ጢሞቴዎስ ዐምባገነንትና የኮሌጁ ጉዳይ ምልአተ ጉባኤውን ሲያወያይ ዋለ
  • ሊቀ ጳጳሱ በበላይ ጠባቂነት ተወስነው የሽግግር ዋና ዲን እንዲሾም ሐሳብ ቀርቧል
  • የኮሌጁ ሥራ አመራር ቦርድ ዛሬ ለምልአተ ጉባኤው ማብራሪያ ይሰጣል

His Grace Abune Timothyየቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ከእናት ቤተ ክርስቲያን መዋቅር ወጥተው በገለልተኛ አስተዳደር ለሚመሩ አብያተ ክርስቲያን የአንድነት ጥሪ ሊያስተላልፍ ነው፡፡ ምልአተ ጉባኤው በትላንት፣ ጥቅምት ፲፱ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ውሎው የቤተ ክርስቲያንን አንድነትና መዋቅር ከማጠናከር አንጻር በገለልተኛ አስተዳደር ለሚመሩ አብያተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ ተግባራት መፈጸም እንደሚገባቸው መመሪያ ሰጥቷል፡፡

Continue reading

ሰበር ዜና – የቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ላይ መነጋገር ጀመረ – በገዳማዊ ሕይወት ያልተፈተኑ፣ በዲያቢሎስ ነቀፋና ወጥመድ የወደቁ፣ በፍቅረ ንዋይ እና በፍቅረ ሢመት ያበዱ፣ የውድቀት ታሪክ የሞላቸው፣ በውጭ ባሉ ሰዎች ክሥና ስሞታ እንጂ መልካም ምስክር የማይሰማባቸው፣ በአገልግሎት ያልተፈተኑ ሰዎችን መሾም አደጋው የበዛ ነው!!

  • ምልአተ ጉባኤው አስመራጭ ኮሚቴ እንደሚሠይም ይጠበቃል፤ አስመራጭ ኮሚቴው በየአህጉረ ስብከቱ ሊቃነ ጳጳሳትና የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሚቀርቡ የዕጩ ኤጲስ ቆጶሳትን ጥቆማ ያሰባስባል፡፡ በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ ፲፰ በተደነገገው መሠረት በአስመራጭ ኮሚቴው በዕጩነት ተመርጠው ከቀረቡት ቆሞሳት መካከል በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ ፭ ቁጥር ፺ – ፺፭ እንደታዘዘው ተሿሚ ዕጩ ኤጲስ ቆጶሳት በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በድምፅ ብልጫ ይመረጣሉ፤ ተወዳዳሪዎች ያገኙት ድምፅ እኩል ከኾነ ዕጣ የወጣለት ቆሞስ ኤጲስ ቆጶስ ኾኖ ይሾማል፡፡
  • በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት ተቀብተው የሚሾሙት ኤጲስ ቆጶሳት የሚመደቡባቸው ዘጠኝ/ዐሥር አህጉረ ስብከት÷ ሽሬ እንዳሥላሴ፣ አክሱም፣ ዋግ ኽምራ፣ መተከል፣ ጋምቤላ፣ ወላይታ፣ ዳውሮ፣ ጉራጌ እና ጉጂ ቦረ እንደሚኾኑተጠቅሷል፡፡ በአንድ ቤተ ጉባኤ/የአብነት ትምህርት/ ምስክርነት ማግኘትና የሚሾሙበትን ሀ/ስብከት አካባቢ ቋንቋ መናገር መሠረታዊ የመምረጫ መስፈርቶች እንደኾኑ ተገልጧል፡፡

Continue reading